አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ 3፡00 - 11:00
info@esacademy.gov.et |

የብስክሌት ዲፓርትመንት

የብስክሌት ዲፓርትመንት ጠንካራ እና ተወዳዳሪ ብስክሌተኞችን ለማፍራት የኢትዮጵያን ልዩ ልዩ መልከዓ ምድሮች ጥቅም ላይ ያውላል። የብርታት እና የፍጥነት ሥልጠናዎችን በመጠቀም አትሌቶች በከፍተኛ ደረጃ እሽቅድምድሞች ውስጥ ለመሳተፍ የሚያስፈልገውን ጽናት እና ጥንካሬ ይጎናጸፋሉ። ይህ ዲፓርትመንት ቴክኒካዊ የቭስክሌት ክህሎቶችንም በማስተማር አትሌቶች አፈጻጸማቸውን እያሻሻሉ የተለያዩ መልከዓ ምድሮች ላይ መንዳት እንዲችሉ ያዘጋጃል። እጅግ ዘመናዊ መሣሪያዎች እና የተራቀቁ የስልጠና መገልገያዎች አትሌቶች ለስኬት የሚያስፈልጋቸውን ነገሮች ሁሉ ያቀርባሉ። የብስክሌት ዲፓርትመንት አትሌቶችን ለኦሎምፒክ ውድድር ጨምሮ ለተለያዩ አካባቢያዊ፣ ክልላዊ እና ዓለም አቀፍ ውድድሮች ማዘጋጀት ላይ ጥብቅ ትኩረት በማድረግ የዓለም መድረክ ላይ ውጤት ለማምጣት ዝግጁ የሆኑ የቀጣዩን ትውልድ የኢትዮጵያ የብስክሌት ሻምፒዮኖች የማፍራት ሥራን እየመራ ይገኛል።

Related Post

የአትሌቲክስ ዲፓርትመንትየአትሌቲክስ ዲፓርትመንት

የአትሌቲክስ ዲፓርትመንት የኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ መሠረት ሲሆን፣ ኢትዮጵያ በረጅም ርቀት ሩጫ እና በትራክ እና መስክ ውድድሮች ያላትን ታላቅ ታሪክ በኩራት ወደፊት ያራምዳል። በተራቀቁ የስልጠና ስልቶች ላይ የሚያተኩረው ይህ ዲፓርትመንት አፈጻጸምን ለማሻሻል እና የላቀ ደረጃ ላይ ለመድረስ ዘመናዊ የስፖርት ሳይንሶችን

የመረብ ኳስ ዲፓርትመንትየመረብ ኳስ ዲፓርትመንት

የመረብ ኳስ ዲፓርትመንት በቤት ውስጥ እና የባህር ዳርቻ መረብ ኳስ ጨዋታዎች ሁለገብ ስልጠናዎችን በማቅረብ አትሌቶችን ከፍተኛ እንቅስቃሴ ከሚታይባቸው የዓለም ስፖርት መካከል አንዱ በሆነው መረብ ኳስ ለስኬት ያዘጋጃል። ስልጠናው እንደ ሰርቭ፣ ብሎክ እና የመከላከል ቴክኒኮች በመሳሰሉ ወሳኝ ክህሎቶች ላይ ያተኩራል። ይህ ዲፓርትመንት አትሌቶች ሜዳ ላይ ያለምንም ችግር እንደ አንድ ሆነው መሥራት መቻላቸውን ለማረጋገጥ

የዋና ዲፓርትመንትየዋና ዲፓርትመንት

የዋና ዲፓርትመንት ልዩ ቴክኒካዊ ብቃት፣ ብርታት እና የውድድር መንፈስ የተላበሱ አትሌቶችን ለማፍራት የተቋቋመ ነው። ውሃ መቅዘፍ፣ አዟዟር እና አጀማመርን በማዳበር ላይ የሚያተኩረው ይህ ዲፓርትመንት አትሌቶች ውኃ ውስጥ የላቀ ውጤት ማምጣት እንዲችሉ ይረዳል። የጥንካሬ እና የአካል ብቃት ፕሮግራሞች የዋና ውድድር ውስጥ ስኬታማ ለመሆን

amአማርኛ