አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ 3፡00 - 11:00
info@esacademy.gov.et |

የብስክሌት ዲፓርትመንት

የብስክሌት ዲፓርትመንት ጠንካራ እና ተወዳዳሪ ብስክሌተኞችን ለማፍራት የኢትዮጵያን ልዩ ልዩ መልከዓ ምድሮች ጥቅም ላይ ያውላል። የብርታት እና የፍጥነት ሥልጠናዎችን በመጠቀም አትሌቶች በከፍተኛ ደረጃ እሽቅድምድሞች ውስጥ ለመሳተፍ የሚያስፈልገውን ጽናት እና ጥንካሬ ይጎናጸፋሉ። ይህ ዲፓርትመንት ቴክኒካዊ የቭስክሌት ክህሎቶችንም በማስተማር አትሌቶች አፈጻጸማቸውን እያሻሻሉ የተለያዩ መልከዓ ምድሮች ላይ መንዳት እንዲችሉ ያዘጋጃል። እጅግ ዘመናዊ መሣሪያዎች እና የተራቀቁ የስልጠና መገልገያዎች አትሌቶች ለስኬት የሚያስፈልጋቸውን ነገሮች ሁሉ ያቀርባሉ። የብስክሌት ዲፓርትመንት አትሌቶችን ለኦሎምፒክ ውድድር ጨምሮ ለተለያዩ አካባቢያዊ፣ ክልላዊ እና ዓለም አቀፍ ውድድሮች ማዘጋጀት ላይ ጥብቅ ትኩረት በማድረግ የዓለም መድረክ ላይ ውጤት ለማምጣት ዝግጁ የሆኑ የቀጣዩን ትውልድ የኢትዮጵያ የብስክሌት ሻምፒዮኖች የማፍራት ሥራን እየመራ ይገኛል።

Related Post

የዋና ዲፓርትመንትየዋና ዲፓርትመንት

የዋና ዲፓርትመንት ልዩ ቴክኒካዊ ብቃት፣ ብርታት እና የውድድር መንፈስ የተላበሱ አትሌቶችን ለማፍራት የተቋቋመ ነው። ውሃ መቅዘፍ፣ አዟዟር እና አጀማመርን በማዳበር ላይ የሚያተኩረው ይህ ዲፓርትመንት አትሌቶች ውኃ ውስጥ የላቀ ውጤት ማምጣት እንዲችሉ ይረዳል። የጥንካሬ እና የአካል ብቃት ፕሮግራሞች የዋና ውድድር ውስጥ ስኬታማ ለመሆን

የአትሌቲክስ ዲፓርትመንትየአትሌቲክስ ዲፓርትመንት

የአትሌቲክስ ዲፓርትመንት የኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ መሠረት ሲሆን፣ ኢትዮጵያ በረጅም ርቀት ሩጫ እና በትራክ እና መስክ ውድድሮች ያላትን ታላቅ ታሪክ በኩራት ወደፊት ያራምዳል። በተራቀቁ የስልጠና ስልቶች ላይ የሚያተኩረው ይህ ዲፓርትመንት አፈጻጸምን ለማሻሻል እና የላቀ ደረጃ ላይ ለመድረስ ዘመናዊ የስፖርት ሳይንሶችን

የጠረንጴዛ ቴኒስ ዲፓርትመንትየጠረንጴዛ ቴኒስ ዲፓርትመንት

የጠረጴዛ ቴኒስ ዲፓርትመንት አትሌቶች ውስጥ ትኩረት፣ ቅልጥፍና እና ስትራቴጂካዊ አስተሳሰብን በማዳበር እጅግ አጣዳፊ ከሚባሉት መካከል አንዱ በሆነው ስፖርት ውስጥ ስኬታማ መሆን እንዲችሉ ይረዳል። የዲፓርትመንቱ ስልታዊ የስልጠና ፕሮግራም ፈጣን ምላሽ የመስጠት ችሎታን፣ የእጅ እና ዓይን ቅንጅትን እና እንደ ቆረጣ፣ ሰርቭ እና የእግር ሥራ የመሳሰሉ የተራቀቁ ቴክኒኮችን ያዳብራል። አትሌቶች ከቴክኒካዊ ክህሎቶች በተጨማሪ

amአማርኛ