አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ 3፡00 - 11:00
info@esacademy.gov.et |
All Day

ወርልድ ቴክዋንዶ ሻምፒዮና

የኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ አዳራሽ Bole, Addis Ababa

የኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ የአትሌቲክስ ልህቀት እና የባህል አንድነት በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚከበሩበትን ወርልድ ቴኳንዶ ሻምፒዮና ለማስተናገድ ዕድሉን በማግኘቱ በጣም ደስተኛ ነው። ይህ ታላቅ ዝግጅት የስፖርቱን ኃይል፣ ትኩረት እና ዲሲፕሊን በሚያሳዩ ውድድሮች ላይ እንዲሳተፉ በዓለም ዙሪያ የሚገኙ ታላላቅ የቴኳንዶ አትሌቶችን ያሰባስባል። ከፍተኛ ደረጃ ያላቸው መገልገያዎች እና ደማቅ ድባብ ያለው ይህ ሻምፒዮና የስፖርታዊ ጨዋነት እና የዓለም አቀፍ ትብብር መዘክር መሆኑ አይቀሬ ነው። ታዳሚዎች ከውድድሩ ባሻገር የባህል ኤግዚቢሽኖችን የመጎብኘት፣ በባለሙያዎች የሚመሩ አውደጥናቶች ላይ የመሳተፍ እና ከዓለም አቀፍ አሸናፊዎች ጋር የመተዋወቅ ዕድል ያገኛሉ።

መግቢያ በነፃ
Ongoing

አትሌቲክስ ሻምፒዮና

የኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ ግቢ፣ Cmc road, Addis Ababa

የኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ ከቀጠናው እና ከዚያም ባሻገር የላቁ አትሌቶችን በማሰባሰብ ፍጥነት፣ ጥንካሬ እና ብርታት በሚተዋወቅበት ውድድር የሚያሳትፈውን የአትሌቲክስ ሻምፒዮና እንደሚያስተናግድ ሲያበስር በደስታ ነው። ልብ አንጠንጣይ ከሆኑ የአጭር ርቀት እና የረጅም ርቀት ውድድሮች ጀምሮ እስከ ዝላይ እና አሎሎ ውርወራ ድረስ የሚካሄድበት ይህ ዝግጅት ታላቅነትን ዒላማ አድርገው የሚሰሩት ተሳታፊዎች ያላቸውን አስደናቂ ተሰጥዖ እና ቁርጠኝነት ያሳያል። እጅግ ዘመናዊ መገልገያዎች እና ድጋፍ የተሞላበት ድባብ ያለው ውድድር አዳዲስ ክብረ ወሰኖችን ማስፈር ብቻ ሳይሆን ለቀጣዩ ትውልድ አትሌቶች ተነሳሽነት እንደሚሰጥም እርግጥ ነው። የአትሌቲክስ ልህቀት መንፈስ እና የስፖርታዊ ጨዋነትን በምናከብርበት ሊታለፍ የማይገባ ዝግጅት ይቀላቀሉን!

amአማርኛ